ከ4ሺህ 500 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የፈርዖን ‹ሶላር ጀልባ› ወደ ግብፅ ሙዚየም ተዛወረ

ከ4 ሺህ 500 ዕድሜ በላይ ያስቆጠረና በፈርዖኖች የተገነባ አንድ አስደናቂ ጥንታዊ የግብፅ ጀልባ በጊዛ በሚገኘው በታላቁ የግብፅ ሙዚየም እንዲዛወር ተደርጓል።

ጀልባውን የሰራው ከ 2,589-2,566 ዓመተ ዓለም እንደ ነገሠ የሚታመነው ንጉሥ ኩፉ ሲሆን በጥንቶቹ ግሪኮች ቺዮፕስ በመባል ይታወቅ ነበር

የፎቶው ባለመብት, Egyptian Ministry of Tourism and Antiquity

የምስሉ መግለጫ, የንጉስ ኩፉ ታላቁ ጀልባ ከ 4,500 ዓመታት በላይ ዕድሜ ያለው ሲሆን በ አውሮፓውያኑ 1954 ሲገኝም ሙሉ በሙሉ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደነበረ ነው

የፎቶው ባለመብት, Egyptian Ministry of Tourism and Antiquity

የምስሉ መግለጫ, የጣውላ ጀልባውን ወደ አዲሱ ቋሚ ማሳያ ሙዚየሙ ለማንቀሳቀስ ትልልቅ ማሸኖችን ተጠቅመዋል

የፎቶው ባለመብት, Egyptian Ministry of Tourism and Antiquity

የምስሉ መግለጫ, የሶላር (የፀሃይ ጀልባ) የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ጀልባ ፈርዖኑ ከሞተ በኋላ በሰማይም እንዲንቀሳቀስ ለማስቻልም የሚል ፅንሰ ሃሳብን የያዘ ነው።

የፎቶው ባለመብት, Egyptian Ministry of Tourism and Antiquity

የምስሉ መግለጫ, ጀልባው የተገኘው በካይሮ ውስጥ በሚገኘው ታላቁ ፒራሚድ ጊዛ ሲሆን የተገነባውም በንጉስ ኩፉ ነው

የፎቶው ባለመብት, Egyptian Ministry of Tourism and Antiquity

የምስሉ መግለጫ, መርከቡ በግብፅ ባለሥልጣናት ዘንድ በሰው ታሪክ ውስጥ ከእንጨት የተሠራ "ትልቁ እና በጣም ጥንታዊ" ቅርስ ነው ተብሏል።

የፎቶው ባለመብት, Egyptian Ministry of Tourism and Antiquity

የምስሉ መግለጫ, ከ 2,589-2,566 ዓመተ ዓለም እንደ ነገሠ የሚታመነው ንጉሥ ኩፉ - በጥንቶቹ ግሪኮች ቺዮፕስ በመባል ይታወቅ ነበር