
የፎቶው ባለመብት, Shutterstock
የምስሉ መግለጫ, በኢራን በተፈጸመ ጥቃት የፈረሰ የመኖርያ ሕንጻመቀመጫውን አሜሪካ ያደረገው የሰብዓዊ መብቶች አክቲቪስቶች ዜና ወኪል ሃራና፣ አንድ
ወሩን ዛሬ በያዘው የኢራን ጦርነት 217 ሕጻናትን ጨምሮ 1464 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ዘግቧል።
አሜሪካ እና እስራኤል በቴህራን ላይ ጦርነት የከፈቱት የካቲት 21 2018 ዓ.ም.
ነበር።
የእስራኤል መከላከያ ከ12ሺህ በላይ ቦምቦችን በመላ ኢራን መጠቀሙን ሲገልጽ በቴህራን
ብቻ 3,600 ተጠቅሞ ድብደባ ፈጽሟል።
አሜሪካ እንዲሁ በመላ ኢራን ከ9ሺህ በላይ ዒላማዎችን በመለየት ድብደባ መፈጸሟን ገልጻለች።
አሜሪካ እና እስራኤል ዒላማ አድርገው ድብደባ የፈጸሙባቸው አብዛኛዎቹ ፖሊስ ጣቢያዎች፣
ወታደራዊ እና ፖሊስ ዩኒቨርስቲዎች፣ የፖሊስ ዋና መሥሪያ ቤት፣ የመጠለያ ቤቶች፣ የአብዮታዊ ዘብ ቤቶች፣ እንዲሁም ኬላዎች እና
የጦር መሣሪያ ማከማቻዎች ይሆናሉ ተብለው የሚታሰቡ ስፈራዎች እንደሆኑ ዘገባው ያስረዳል።
እነዚህ ዒላማዎች ብዙ ጊዜ የሚገኙት ሰላማዊ ሰዎች በሚኖሩባቸው እና እንቅስቃሴዎች
በሚበዛባቸው አካባቢዎች ነው።
በኢራን ጥቃት ሲፈጸም የተመለከተ ነዋሪ ለቢቢሲ እንደተናገረው በሰላማዊ ሰዎች መኖሪያ የሚፈጸሙ ድብደባዎች የመንግሥት ተቃዋሚ የነበሩትን ሁሉ ያስቆጣ ነው።
ቢቢሲ በሪፖርቱ ላይ ስለተገለጹት የሰላማዊ ሰዎች መኖሪያዎች ለእስራኤል ጦር ጥያቄ ቢያቀርብም ጥቃቶቹ መፈጸማቸውን ከማረጋገጥ ውጪ ተጨማሪ ምላሽ ሳይገኝ ቀርቷል።
የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ለጥያቄዎቹ ምላሽ አልሰጠም።
ኢራን በጦርነቱ ውስጥ የአሜሪካ አጋር በሆኑት የባሕረ ሰላጤው አገራት የሚገኙ አውሮፕላን
ማረፊያዎችን፣ ሆቴሎችን እንዲሁም የሰላማዊ ዜጎች መኖሪያዎችን እና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን አጥቅታለች።
በኢራን የኢንተርኔት እና የኮሚኒኬሽን አገልግሎት በተቋረጠበት ሁኔታ በርካቶች ቀጣዩ
የጥቃት ዒላማ የቱ እንደሚሆን ለማወቅ እንደማይችሉ በመግለጽ ፍርሃታቸውን ያስረዳሉ።