በእየሩሳሌም የኢትዮጵያውያን የትንሳዔ በዓል አከባበርና ከአህጉሪቱ የተመረጡ የሳምንቱ ፎቶዎች

ባለፈው ሳምንት እሁድ የትንሳዔ ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን በእየሩሳሌም ነዋሪነታቸውን ያደረጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮችም እለቱን በዴር ሱልጣን ገዳማት በደመቀ ሁኔታ አክብረውታል።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በእየሩሳሌም የነበረው የኢትዮጵያውያን የትንሳኤ በዓል አከባበርን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ያገኘናቸው የሳምንቱ ፎቶዎች እነሆ!

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, ባለፈው ሳምንት እሁድ የትንሳዔ ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን በእየሩሳሌም ነዋሪነታቸውን ያደረጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮችም ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረውታል። የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ቅዳሜ እለት በዝማሬና በሽብሸባ የእየሱስ ክርስቶስን ትንሳዔ እንዲህ አስበውታል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, ባለፈው ሳምንት እሁድ የትንሳዔ ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን በእየሩሳሌም ነዋሪነታቸውን ያደረጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮችም ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረውታል። ቅዳሜ ሌሊትም በእየሩሳሌም የነበረው የቅዳሴ ስነ ስርዓትም ይህንን ይመስል ነበር

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, ባለፈው ሳምንት እሁድ የትንሳዔ ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን በእየሩሳሌም ነዋሪነታቸውን ያደረጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮችም ቀኑን በደመቀ ሁኔታ አክብረውታል። በእየሩሳሌም በሚገኘው የዴር ሱልጣን ገዳም ቅዳሜ ሌሊትን በቅዳሴና በጸሎት አሳልፈውታል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ሳምንት ረቡዕ በደቡብ አፍሪካዋ ሶዌቶ 'ሚስ ፍሪደም' የፋሽን ትርዒት የተካሄደ ሲሆን ከመድረክ ጀርባም የነበረው የጸጉር ስራ ይህንን ይመስል ነበር።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ሳምንት ረቡዕ በደቡብ አፍሪካዋ ሶዌቶ የተካሄደው 'ሚስ ፍሪደም' የፋሽን ትርዒት

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ወር በበደቡብ አፍሪካ ኩዋዙሉ-ናታል ግዛት አደገኛ ጎርፍ ተከስቶ የበርካታ ሰዎችን ህይወት ቀጥፏል። ከሰሞኑም የቀብር ስነ ስርዓታቸው ተካሂዷል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ሳምንት ረቡዕ በግብፅ መዲና ካይሮ የሚገኙ ሙስሊሞች ረመዳንን ፆም በአል አዝሃር መስጂድ በስግደት አሳልፈውታል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በግብፅ መዲና ካይሮ የሚገኘው አል አዝሃር መስጂድ በያዝነው ሳምንት

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በሱዳን ካርቱም በኪነ ጥበብ ህንጻ ከፍተኛ ስፍራ ካለቸው መስጊዶች አንዱ

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, ባለፈው ሳምንት እሁድ በኡጋንዳ ካምፓላ ለአለም አቀፉ ራግቢ ውድድር ጋናና ሴኔጋል ያደረጉት ፍልሚያ

የፎቶው ባለመብት, EPA

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ሳምንት ሰኞ በናይጄሪያዋ መዲና ሌጎስ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የስራ ማቆም አድማ ምክንያት መዘጋታቸውን በመቃወም በተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ልጇን በጀርባዋ አዝላ የተገኘች ሴት