በግብፅ የኢትዮጵያውያን ሆሳዕና በዓል አከባበርና ከአህጉሪቱ የተመረጡ የሳምንቱ ፎቶዎች

ባለፈው ሳምንት እሁድ የሆሳዕና ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን በግብፅ ነዋሪነታቸውን ያደረጉ ኢትዮጵያውንም ቄጠማ በማሰር ዕለቱን ዘክረውታል።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ በግብፅ የኢትዮጵያውያን የሆሳዕና በዓል አከባበርን ጨምሮ ከአህጉሪቱ ያገኘናቸው የሳምንቱ ፎቶዎች እነሆ!

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, ባለፈው ሳምንት እሁድ የሆሳዕና ክብረ በዓል የተከበረ ሲሆን በግብፅ ነዋሪነታቸውን ያደረጉ ኢትዮጵያውንም ቄጠማ በማሰር በስምዖን ቤተ ክርስቲያን ዕለቱን ዘክረውታል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ሳምንት ረቡዕ የግብፅ ባህላዊ ቡድን ታኑራ የተሰኘውን ባህላዊ ጭፈራ በካይሮ በሚገኘው በኤል-ጉሪ የባህል ቤተ መንግስት ቅዱስ ተብሎ በሚጠራው ረመዳን ወር አቅርበዋል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, በያዝነው ሳምንት ሰኞ በሴራሊዮን ዋና ከተማ ፍሪታውን የስካውት ቡድን ባንድ አባላት በሉምሌይ ባህር ዳርቻ የሙዚቃ ዝግጅታቸውን አቅርበዋል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ቄስ በካይሮ፣ ግብፅ ሞካትታም ተራራ አካባቢ በሚገኘው ሳማን ኤል-ካራዝ ገዳም የሆሳእና በዓልን በቅዳሴ አገልግሎት

የፎቶው ባለመብት, Moses Sawasawa

የምስሉ መግለጫ, በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ምስራቃዊ የናይራጎንጎ ተራራ የተነሳው የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ አንድ አመትን ያስቆጠረ ሲሆን ኩሊኮ የተሰኘው የአርቲስቶች ስብስብ ከዚህ ፍንዳታ ተርፈው በጎማ ካምፕ ውስጥ ለሚኖሩ ግለሰቦች ገንዘብ ለማሰባሰብ የፋሽን ትርኢት አዘጋጅቷል።

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, ባለፈው ሳምንት እሁድ የፋሲካ በዓል በተለያዩ አገራት የተከበ ሲሆን የሴራሊዮን ማሮን ምእመናን 230 አመት እድሜ ባስቆጠረው ዕድሜ ጠገቡ ቤተክርስቲያን በአገልግሎት አክብረውታል።

የፎቶው ባለመብት, Getty Images

የምስሉ መግለጫ, በካይሮ በረመዳን ወር በአል-ማትሪያህ ወረዳ ኢዝቤት ሃማዳ በተካሄደው የኢፍጣር ፕሮግራም ሙስሊሞች በ750 ሜትር ጠረጴዛ ዙሪያ በጅምላ በመሰብሰብ ማዕድ ቆርሰዋል።

የፎቶው ባለመብት, EPA

የምስሉ መግለጫ, በአቢጃን፣ አይቮሪ ኮስት ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለት ለማስታወስ በመስቀል ላይ ሲሰቀል።

የፎቶው ባለመብት, Reuters

የምስሉ መግለጫ, በአቢጃን፣ አይቮሪ ኮስት ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለት ለማስታወስ በመስቀል ላይ እየተቸነከረ ያለ ግለሰብ

የፎቶው ባለመብት, AFP

የምስሉ መግለጫ, በጎ ፈቃደኞች በደርባን በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በተነሳው ጎርፍ የጣላቸውን ዛፎች ሲያጸዱ