ለጉብኝት ክፍት የተደረገው የቀድሞው ማዕከላዊ እሥር ቤት በፎቶ
የቀድሞው ማዕከላዊ እሥር ቤት ዛሬ ለጉብኝት ክፍት ተደርጓል። ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2011 ዓ. ም. እሥር ቤቱ ለሕዝብ እይታ ክፍት እንደሚሆን የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አስታውቋል።
ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈጸምበት ነበር የሚባለው ማዕከላዊ እሥር ቤት፤ ጳጉሜን 5 ቀን 2011 ዓ. ም. የሚከበረውን የፍትህ ቀን ምክንያት በማድረግ ለሕዝብ እይታ ክፍት መደረጉንም የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አስታውቋል።
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ እሥር ቤቱን ጎብኝተዋል።
በቦታው የሚገኘው ባልደረባችን ካነሳቸው ፎቶግራፎች ጥቂቱን እናካፍላችሁ፦
እንዳያመልጥዎ
ከየፈርጁ
በስፋት የተነበቡ
የሚፈልጉት ይዘት የለም
{{rankTranslation}}