''ምንም አንኳን ኦሮሚያ ለፎቶግራፍ ምቹ ብትሆንም በፎቶግራፍ ትዕይንት ወደ ኋላ ቀርተናል''

የኦሮሚያን ገጸ-ምድር፣ የጎብኝት መዳረሻዎች እና የኦሮሚያን ባህል ያሚያሳየው የፎቶግራፍ ትዕይንት በአዲስ አበባ የኦሮሞ ማዕከል ለእይታ ቀርቧል።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, የቦረና ሴቶች በቅቤና በተለያዩ የውበት መጠበቂያዎች እራሳቸውን ያስውባሉ። ይሀ ፎቶግራፍ የተነሳው በቦረና ዞን አሬሮ ከተማ አቅራቢያ ነው።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, በአዲስ አበባ ዙሪያ ካሉ አርሶ አደሮች መካከል ይህ ወጣት ያጨደውን ስንዴ ሲያስር።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, ክረምቱ ካለፈ በኋላ ከኦሮሚያ የተለያዩ አቅጣጫዎች በመሰባሰብ ለፈጣሪያቸው 'ዋቃ' ምስጋናን ያደርሳሉ። እነዚህ እናቶች ከአርሲ ዞን ወደ ቢሾፍቱ የኢሬቻ በዓል ለማክበር የመጡ ናቸው።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, ይህ ፎቶ የገጠሪቷን ኦሮሚያ ህይወት በከፊል የሚያሳይ ነው። ቦታው ሊበን ጉጂ ዞን ውስጥ ነው።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, ለቦረና ኦሮሞ ፍየሎች ከፍተኛ ቦታ አላቸው። ፍየሎች በአነስተኛ ውሃና የግጦሽ ሣር ድርቅን መቋቋም ይችላሉ። አጋዘን ወይም ፍየል የሚመስለው ዛፍ የተነሳው ያቤሎ ቦረና ነው።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, እንደሌሎቹ የኦሮሞ ጎሳዎች ከረዩዎች የራሳቸው የሆነ ቦኩ የተባለ የገዳ ሥርዓታ አላቸው። የመጨረሻው የቦኩ የሥልጣን ርክክብ የተካሄደው በ2009 ዓ.ም. ታሬ ሉጎ በምትባል መተሃራ አካባቢ በምትገኝ ቦታ ነው።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, ንጉስ አባ ጅፋር ከ1878 – 1932 ጅማና አከባቢዋን አስተዳድረዋል። ይህ ቤተ-መንግሥታቸውም በጅማ ከተማ ኦልከዓ በሚባል አከባቢ ይገኛል።

የፎቶው ባለመብት, AMENSISA IFA

የምስሉ መግለጫ, የምስጥ ኩይሳዎች በረሃማ በሆኑ እንደ ቦረና ባሉ አካባቢዎች ላይ ማየት የተለመደ ነው።