በአዲስ አበባ በእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ የተዘጋጀው የጎዳና ላይ ታላቅ ኢፍጣር በምሥል

በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ሥነ ሥርዓት በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊሞች ተገኝተው ታድመዋል። የከተማዋ አስተዳደርም መርሃ ግብሩ በሰላም መጠናቀቁን እና ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የተወከሉ እንግዶች እንደተገኙበት አስታውቋል።

የፎቶው ባለመብት, MayorOfficeAA

የምስሉ መግለጫ, በአዲስ አበባ በእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ የተዘጋጀው የጎዳና ላይ ታላቅ የኢፍጣር መርሃ ግብር በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል

የፎቶው ባለመብት, MayorOfficeAA

የምስሉ መግለጫ, በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ የሚኖሩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ የተዘጋጀው የጎዳና ላይ ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም ትናንት ምሽት ተካሄዷል

የፎቶው ባለመብት, Anadolu Agency

የምስሉ መግለጫ, በታላቁ የጎዳና የኢፍጣር ሥነ ሥርዓት ላይ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊሞች ታድመዋል።

የፎቶው ባለመብት, AMANUEL SILESHI

የምስሉ መግለጫ, አርብ ምሽት በመስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር ላይ የተካፈሉ ሙስሊም ሴቶች

የፎቶው ባለመብት, AMANUEL SILESHI

የምስሉ መግለጫ, በመስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር የተገኙ ሙስሊሞች ሲሰግዱ

የፎቶው ባለመብት, AA City Mayor

የምስሉ መግለጫ, በትናንትናው ዕለት በመስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር ሥነ ሥርዓት ላይ ለመካፈል ከመጡት መካከል የኢትዮጵያ ባንዲራ ይዘው የታዩ ይገኙበታል።

የፎቶው ባለመብት, AMANUEL SILESHI

የምስሉ መግለጫ, በትናንትናው ዕለት በመስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር ሥነ ሥርዓት ላይ ለመካፈል ከመጡት መካከል የፍልስጤም ባንዲራ ይዘው የታዩ ይገኙበታል።

የፎቶው ባለመብት, AMANUEL SILESHI

የምስሉ መግለጫ, በትናንትናው ዕለት በመስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር ስነስርዓት ላይ ለመካፈል ከመጡት መካከል በጎንደር ከቀብር ስነስርዓት ጋር በተያያዘ በተነሳ ጠብ ምክንያት ሙስሊሞች መገደላቸውን በማውገዝ መፈክር የያዙ ይገኙበታል

የፎቶው ባለመብት, MayorOfficeAA

የምስሉ መግለጫ, በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በተካሄደው ታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነስርዓት በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊሞች ተገኝተው ሲሰግዱ